Skip to main content

የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ ከ100 የሚበልጥ የምርምር ፕሮጀክቶች እያካሄደ ነው





አዋሳ, ህዳር 28 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ችግር ፈቺ የሆኑ ከ100 የሚበልጡ የምርምር ፕሮጀክቶች እያካሄደ መሆኑን የዩኒቨርስቲው የምርምር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ገለጹ።

ዳይሬክቴሩ ዶክተር ተስፋዬ አበበ ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ በተካሄደ የምርምር ስራ ግምገማ አውደ ጥናት ላይ እንዳስታወቁት የምርምር ፕሮጀክቶቹ በተለይ ሀገሪቱ ለተያያዘችው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን የልማት ፕሮግራም ስኬት የበኩላቸውን አሰተዋጾኦ የሚያበረክቱ ናቸው፡፡
ቀደም ብሎና ዘንድሮ የተጀመሩት የምርምር ፕሮጀክቶች በግብርና ፣ በተፈጥሮ ሀብት ፣ በደን ልማት ፣ በእንስሳት ልማት፣ በጤናና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የምርምር ስራዎቹ የሚካሄዱት ከደቡብ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር በሀዋሳ ከተማና ዙሪያ፣ በቦርቻ ፣ በወንዶ ገነት፣በዳሌ ፣በሃገረ ሰላምና ሌሎች አካባቢዎች መሆኑን ጠቁመው በዩኒቨርስቲው የሚያስተምሩ የየዘርፉ ምሁራንና ተመራቂ ተማሪዎችን በማንቀሳቀስና ህብረተሰቡን በማሳተፍ ሁሉንም የልማት መስኮችን የዳሰሱ ችግር ፈቺ መሆናቸውን ገልጠዋል፡፡
በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በግብርናው ዘርፍ ለዝናብ አጠር አካባቢ ተስማሚና ውጤታማ የሆኑ አዳዲስ የበቆሎ የእንሰት ፣የስራ ስርና ሌሎች የምግብ ሰብል ዓይነቶች በምርምር በማውጣት ለተጠቃሚው ለማድረስ በሂደት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
የዩኒቨርስቲው ፕሬዜዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በበኩላቸው የመማር ማስተማሩን ስራ በጥራትና በፍትሃዊነት ከማራመድ ጎን የሚካሄደው ምርምር ከውጪ ሀገራት መሰል የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን ገልጸዋል።
ምርምሮችን በማስፋትና ግኝቶችን ወደ ምርት ስራ በማሸጋገር የተሻለ ለውጥና ዕድገት ለማምጣት በትኩረት እየሰሩ እንደሆነ ማስታወቃቸውን የዩኒቨርስቲው ማርኬትንግና ኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገልጿል፡፡

Comments

Popular Posts

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል  የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡  የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡  ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡  ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ  መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል

Sidama: the Luwa and the Anga Culture and their Social Implications

By Wolassa Kumo 1. Introduction In my previous articles, I mentioned the Sidama grand social constitution Seera, and various sub constitutions which derive from this grand constitution. We have also seen that all social constitutions or Seera in Sidama were based on the Sidama moral code of halale, the true way of life. In this socio-cultural and socio-political system, the role of the elders was very important. Elders were bestowed with the power of enforcing the Seera and referring the recalcitrant to Magano or God if he/she refuses to abide by the Seera. The power of elders in the Sidama society was not based on a simple age count as is the case in most modern societies. The Sidama elder is more the product of various social processes through which he passes than the product of a simple aging. For a person to become a recognised elder with authority in Sidama, he has to become a Cimeessa (respected elder with authority) or Cimeeyye for many respected elders. There are three importa