በደቡብ ክልል የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የ13 ሆቴል ባለንብረቶችን በተጨማሪ እሴት ታክስ (በቫት) ማጭበርበር በመጠርጠራቸው በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ታወቀ፡፡ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ባለሆቴሎች መካከል የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ማረጋጫ ሰርተፍኬት ያላቸው ይገኙበታል፡፡ የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የመናኸሪያ ክፍለ ከተማ አዛዥ ኢንስፔክተር በየነ ባናታ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የሆቴል ባለንብረቶቹና ተወካዮቻቸው የተያዙት ለመንግሥት ማስገባት የነበረባቸውን ተጨማሪ እሴት ታክስ በማጭበርበር ተጠርጥረው ነው፡፡ ኢንስፔክተር በየነ እንደሚሉት፣ በመናኸሪያ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የብሉ ናይል፣ የታደሰ እንጆሪ፣ የሲዳማ ውበት ሆቴሎች ሥራ አስኪያጆችና ገንዘብ ተቀባዮች በአጠቃላይ አሥር ሰዎች /አራት ሴትና ስድስት ወንድ/፤ እንዲሁም የሐሮኒ ኢንተርናሽናል፣ የኢቪኒንግ ስታር፣ የበሹ ጫምበላላ፣ የሻሸመኔ ሪፍት ቫሊ፣ የወላይታ ሶዶና የአርባ ምንጭ ቱሪስት ሆቴሎች ኃላፊዎችና ገንዘብ ተቀባዮች ናቸው፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የሻሸመኔ ሪፍት ቫሊ፣ የወላይታ ሶዶና የአርባ ምንጭ ቱሪስት ሆቴሎች ባለንብረቶች በተመሳሳይ የደረሰኝ ቁጥር ቫት ሲሰበሰቡ ቆይተው ለመንግሥት ገቢ ማድረግ የሚገባቸውን አሥራ ሁለት ሚሊዮን ብር ማጭበርበራቸው በጥቆማ ተደርሶባቸው መሆኑን፣ የእነዚሁ ሆቴሎች ባለሀብቶች በደረጃ አንድ የኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሠማሩና በተመሳሳይ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ናቸው፡፡ የብሉ ናይል፣ የኢቪኒንግ ስታር፣ የሲዳማ ውበት፣ የቤራ፣ የዳህላክና የታደሰ እንጆሪ ሆቴሎች ባለቤቶች በመሰወራቸው ሥራ አስኪያጆችና ገንዘብ ተቀባዮች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ምንጮች ለሪፖርተር አክለው ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ የአሥ
የለበሰው ያደፈ ቁምጣና ሹራብ ከቅዝቃዜው አላዳነውም፡፡ ካፊያው ልብሱን አርሶታል፡፡ ሽው እያለ ከሐይቁ የሚነሳው ነፋስ የሚፈጥረው ቅዝቃዜ ያንቀጠቅጠዋል፡፡ የተጫማው ያረጀ ሲሊፐር እግሩን ከምንም አላዳነውም፡፡ በባዶ እግሩ የሚራመድ ያህል ጨቅይቷል፡፡ ተደባዳቢ ይመስል ፊቱ የተሞነጫጨረ ነው፡፡ ገና 12 ዓመቱ ቢሆንም፣ ቁመናው እንደ ትልቅ ሰው ግዙፍ ነው፡፡ የሚለብሰውን እንደ ልቡ ባያገኝም፣ የሚያስፈልገውን ነገር ለማሟላት ቤሳቢስቲን የሌላቸው ወላጆቹን አያስቸግርም፡፡ ከቤተሰቦቹ ጋር ከሚኖሩበት ታቦር ተራራ ጀርባ ወዳለው ሐዋሳ ሐይቅ ከወረደ እንኳንስ የራሱን የቤተሰቦቹንም የዕለት ጉርስ የሚሸፍንበት ገንዘብ አያጣም፡፡ የአስጎብኚነት ዕውቀት፣ ከሐይቁም ውስጥ ዓሳ የሚያጠምድበት መረብም ሆነ ፈቃድ የለውም፡፡ ሙሉቀን (ስሙ ተቀይሯል) እና ጓደኞቹ ሐይቁን ለመጎብኘት የሚሄዱ ጎብኚዎች በካሜራቸው ጥሩ ፎቶ እንዲያስቀሩ ድባቡን የማሳመር ሥራ ይሠራሉ፡፡ ካሜራውን ይዞ ቁጭ ብድግ እያለ ጥሩ ፎቶ ለማንሳት ጥረት የሚያደርግ ሲያዩ፣ ቆርጠው የያዙትን የዓሳ ሥጋ ይዘው ጠጋ ጠጋ ይላሉ፡፡ ቁርጥራጩን የዓሳ ሥጋ ምግብ ለሚቀሙት አባኮዳዎች ሻሞ ይላሉ፡፡ የተወረወረላቸውን ቀድመው ለመቅለብ አባኮዳዎቹ ክንፋቸውን እየመቱ ወደ ላይ ብድግ ይላሉ፡፡ የናሽናል ጆግሪፊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ያነሱት ዓይነት ፎቶዎች ሳያስቡት ያነሳሉ፡፡ በሁኔታው ተደስተው ደጋግመው ድንቅ ፎቶዎችን ለመውሰድ ሲዘጋጁ እነ ሙሉቀንም አጀንዳቸውን ይፋ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ አቶ ዳዊት አብርሃም ‹‹አንዱን ዓሳ በአሥር ብር ገዝቼ ነው እንዲህ የማዘጋጀው፤›› በማለት በቅድሚያ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ለቀጣዩ ዜና በዚህ መልኩ እንዲዘጋጁ ካደረጉ በኋላ፣ ሌሎች ሰዎች መቶም ሁለት መቶም ብር እንደሚሰጧቸው ቀለል