አዲስ አበባ፣ህዳር 29 2003 (ሬዲዮ ፋና) አምስተኛው የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአል በዛሬውዕለት በተለያዩ ክልሎችበድምቀት ተከበረ። በዓሉ የተከበረው " የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች እጅ ለእጅ ተያይዘንየአገራችንን ህዳሴ ወደ ማይቀለበስት ደረጃ እናደርሳለን" በሚል መሪ ቃል ነው። በአሉትናንት በተለይ በሃዋሳ ከተማ ሲከበር በበአሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙትየፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ካሳ ተክለብርሃን የኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ስርአት በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ውጤታማ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በበኩላቸው ድህነትን ታግለን ማሸነፍ እንደሚገባ አስታውቀዋል። በበአሉ ላይ የተገኙ የብሄር ብሄረሰብ ተወካዮች ፌዴራላዊ ስርአቱ ተጠቃሚ እያደረገ ያለው ብሄርብሄረሰቦችንና ህዝቦችን መሆኑን ጠቅሰው ህገ መንግስቱን በመጠበቅ ድህነትን ለመዋጋት እንደሚረባረቡ አረጋግጠዋል። በተያያዘምየብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሀገራችን ህዝቦች በመከባበር ላይ የተመሰረተ አንድነታቸውን በማጠናከር ኢትዮጵያንመካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ የገቡትን ቃል ዳግም የሚያድሱበት እንደሆነ የአፋር ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ተናግረዋል። ምክትልርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አወል ወግሪስ ለሬዲዮ ፋና እንዳሉት ቀኑ ህዝቦች ያገኟቸውን ህገ መንግስታዊ መብቶች በመጠቀም ልማትንለማፋጠንም ቃል የሚገቡበት ነው። ለህዝቦች ራስን በራስ ማስተዳደር እንዲሁም በራስ ቋንቋ መማር፣ መስራትና መዳኘት መሰረት ለሆነው ለዚሁ ቀን ከፍተኛ ስፍራ በክልሉ ህዝብ እንደሚሰጠው ገልጸዋል። በተተመሳሳይ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦችን እኩልነትን ለማረጋገጥ የተከፈለውን መስዋዕትነት በመጠበቅ ለሀገራችን ቀጣይ እድገት በጋራ መሰለፍ እንዳለብን የትግራይክልል ርእሰ መስተዳድር ተናግረዋል። ርእሰ መስተዳድሩ አቶ አባይ ወልዱ ዛሬ በመቀሌ በተከበረው የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ላይ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት የተገኙ ድሎችን በመጠበቅና አንድነታችንን በማጠናከር ድህነትን ለማጥፋት ጠንክረን መስራት አለብን ብለዋል። መንግስት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፅድቆ እንቅስቃሴ ማድረግ መጀመሩን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ እቅዱን ተግባራዊለማድረግና የሀገሪቱን ህዳሴ ለማረጋገጥ መረባረብ እንዳለብን አሳስበዋል። በበዓሉ ላይ የከተማው ነዋሪዎች፣ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ በከተማው የሚገኙ የ1ኛና ሁለተኛደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የፖሊስ አባላት ተገኝተዋል። አምስተኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ዛሬ በድሬደዋ ከተማ በሰላማዊ ሰልፍና በተለያዩ ዝግጅቶች በታላቅ ድምቀት ሲከበር ውሏል። በዓሉ በርካታ የድሬደዋ ሕዝብ በተገኘበት በድሬደዋ ስታዲዮም ነው የተከበረው። በበአሉ ላይ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች፣የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወታደራዊሰልፍ፣ የስፖርትና ልዩ ልዩ ትርኢቶችን አቅርበዋል። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባዔ ወይዘሮ ቢፍቱ መሀመድ በዓሉን ስናከብር እየተመዘገበያለውን ሁለንተናዊ ልማት ለማስቀጠል ቃል በመግባት ሊሆን ይገባዋል ብለዋል። በሌላበኩል በዛሬው ዕለት እየተከበረ ያለው የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሀገራችንን አንድነት ለማጠናከር ሚናው ከፍተኛእንደሆነ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሰራተኞች ገልፀዋል። በዚሁወቅት እንዳሉት በዓሉ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦችን አንድነት ከማጠናከር ባሻገር የባህልና እሴት ልውውጥ እንዲኖርየሚያደርግ ነው። ለብሄሮችብሄረሰቦችና ህዝቦች መብት መረጋገጥም ሆነ ለቀኑ መከበር መሰረት የሆነውን የሀገራችን ህገ መንግስት ሁሉም በንቃት ሊጠብቀውእንደሚገባም አሳስበዋል። |
የመንግሥት ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ብሏል የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ለምን ወጣ መባሉ ተገቢ አይደለም - ምርጫ ቦርድ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ ተፅዕኖ ሙሉ ለሙሉ ነፃ መሆኑ ሳይረጋገጥና የምርጫ አፈፃፀም ችግሮች ሳይወገዱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለማወጅ መዘጋጀቱ ተገቢ አይደለም ሲል ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የሚመሩት ኢማዴ-ደህአፓ ተቃወመ፡፡ መንግስት፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየሰጠ ያለው ስልጠና የምርጫ ቅስቀሳ አካል ነው ሲልም ፓርቲው ኮንኗል፡፡ የኢትዮጵያ ማህበረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባስገባው ግልፅ ደብዳቤ፤ ያለፉት አገር አቀፍና የአካባቢ ምርጫዎች ከመካሄዳቸው በፊት በምርጫ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር የሚወያይበት መድረክ እንዲዘጋጅ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም እስካሁን ከቦርዱ የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም ብሏል፡፡ ሃገሪቱ “በአንድ አውራ ፓርቲ” ብቸኛ ቁጥጥር ስር መውደቋ አደገኛና አሳሳቢ ነው ያለው ፓርቲው፤ የመድብለ ፓርቲ ስርአት የመገንባት ተስፋችን ጨርሶ እንዳይከስም ቦርዱ ሃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አሳስቧል፡፡ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ የሚካሄድበትን ሁኔታ ለመፍጠር ገዥው ፓርቲና ሃቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚወያዩበት መድረክ እንዲያመቻች በህግ ስልጣን የተሰጠው ምርጫ ቦርድ የገባውን ቃል በማጠፍ መድረኩን ሳያመቻች የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ ፋይዳ የለውም ብሏል - ፓርቲው፡፡ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በተሻሻለው የምርጫ ህግ፣ ለቦርዱ የተሰጠውን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ የማስተባበር ስልጣን ለመቀማት ታማኝ ፓርቲዎችን በተቃዋሚ ስም አሰባስቦ “የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ” በመፍጠር የምርጫ ውድድር አሯሯጭ አሰልፏል ሲ
Comments
Post a Comment